Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በመዲናዋ የነዳጅ አቅርቦት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት …

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ከነዳጅ አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት የሚያስችል ውይይት ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ ጃንጥራር አባይ፣ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ደስታው መኳንንት (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅና የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች ተገኝተዋል።

አቶ ጃንጥራር አባይ በዚህ ወቅት ÷ የነዳጅ አቅርቦት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ ማወቅ መፍትሄ ለመስጠት መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥር አንስተዋል።

የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገት መሠረት ያደረገ የነዳጅ አቅርቦት መኖሩን ጠቅሰው÷ የሀገር ሃብት የሆነውን ነዳጅ በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡

ችግሩን ለመፍታት በሚቀመጡ አቅጣጫዎች ላይ ርብርብ ማድረግ ይጠይቃል ያሉት ም/ከንቲባው÷ እየተወሰዱ ያሉ ርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል፡፡

በሕገ ወጥ መንገድ ለመሸጥ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በመዲናዋ ለሚስተዋለው የነዳጅ አቅርቦት እጥረት መንስኤ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ በበኩላቸው ÷ከነዳጅ ሥርጭት ጋር ተያይዞ በማደያዎች የሚፈፀሙ ችግሮች በርካታ መሆናቸውን አስረድተዋል፡

ችግሩን ለመፍታት ቢሮው የሚያከናውነውን የቁጥጥር ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

ደስታው መኳንንት (ዶ/ር) ÷ መንግሥት ለነዳጅ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ነዳጅን ወደ ሀገር ውስጥ እያስገባ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በየደረጃው ያለውን ሌብነት ማስቆም እና አስተማሪ ርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።

በየሻምበል ምህረት

Exit mobile version