አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከኢኳቶሪያል ጊኒ ፕሬዚዳንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ንጉሜ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ታዬ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ ከአፍሪካ፣ ካሪቢያን እና የፓስፊክ መንግስታት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን መወያየታቸውን ገልጸዋል፡፡
ውይይቱ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነትና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

