Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)‎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጋር በመሆን የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ አጋርተዋል፡፡

በመላው ኢትዮጵያ በክርስትና ጥላ ውስጥ በሚገኙ ቤተ-እምነቶች ያሉ ክርስቲያኖች የትንሳኤን በዓል በተስፋ፣ በመስዋዕትነት እና በአዲስ መነሳት መንፈስ በአንድነት ያከብራሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ዓመታዊውን የፋሲካ ማዕድ ማጋራት ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር በአንድነት ፓርክ በጋራ መታደማቸው ለእውነተኛው የአንድነት መንፈስ ጉልህ ማሳያ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል።

ከሳምንታት የፆም፣ ጥሞና እና ራስን የመመልከት ጊዜ በኋላ ፋሲካ በእውነተኛ አምልኮ፣ መንፈስን አድሶ፣ ቤቶችንም በደስታ ይሞላል፣ በዘመድ አዝማድ መጠያየቅ እና ማዕድ መካፈልም ፍቅርን እንደሚያዳብር ተገልጿል።

‎በዓለ ትንሳኤው በመላው ኢትዮጵያ የእምነት፣ ቤተሰባዊነት እና የመታደስ መንፈስ የሚታይበት መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሁላችንም በዚህ የትንሳኤ መንፈስ ዛሬም፣ ነገም፣ ሰርክ ቤታችንን፣ ልባችንንም ለተቸገሩ ወገኖች መክፈት አለብን ብሏል፡፡

Exit mobile version