Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በኬፕ ታውን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳንላም ኬፕ ታውን የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸንፈዋል፡፡

በወንዶች አትሌት መሀመድ ኢሳ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ55 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል፡፡

በርቀቱ የተሳተፈው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ይሁንልኝ አዳነ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ውድድሩን ጨርሷል፡፡

በሴቶች ደግሞ አትሌት ደራ ዲዳ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት በመግባት 1ኛ በመሆን አጠናቅቃለች፡፡

በርቀቱ የተሳተፉት ሌሎች ኢትየጵያዊያን አትሌቶች መስታወት ፍቅር እና ዋጋነሽ አማረ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን ጨርሰዋል፡፡

Exit mobile version