አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ንስቲያን ክርስተንሰን ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም፤ በመጪው መስከረም በኢትዮጵያ በሚካሄደው የኖርዲክ – አፍሪካ ኢቪ ላይ በጋራ በሚሰሩ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ምክክር አድርገዋል።
አዲስ አበባ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ኩነቶችን የማስተናገድና በብቃት የመወጣት ልምድ ያካበተችና ተመራጭ እየሆነች መምጣቷን ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አመልክተዋል።
የኖርዲክ – አፍሪካ ኢቪ ጉባኤንም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እናሳካዋለን ብለዋል።

