Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሃሙድ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሃሙድ ጋር ተወያይተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ፥ ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሃሙድ ጋር በኢኮኖሚያዊ ትስስር፣ ደኅንነትና የቀጣናዊ መረጋጋት ዙሪያ በመተማመንና በመከባበር ላይ የተመሠረተ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደናል ብለዋል።

ኢትዮጵያና ሶማሊያ ከድንበር በላይ የሚጋሩት ነገር አለ ፤ እሱም እጅግ ውድ የሆነውን ሕዝባችንን እና የጋራ እጣ ፈንታችንን ነው ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

Exit mobile version