አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ ከሩሲያ ፌዴሬሽን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የልዑክ ቡድናቸው ጋር ተወያይተናል ብለዋል።
ማምሻውን በነበረን የጋራ ጊዜ በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችና አዳዲስ የትብብር ዕድሎች ዙሪያ የተቃኘ ውይይት አድርገናል ነው ያሉት።

