Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ከ157 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ሎጂስቲክስ በ2018 በጀት ዓመት 157 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ፡፡
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አብዱልበር ሸምሱ (ኢ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ÷ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 7 ነጥብ 04 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ጭነት ማጓጓዝ ተችሏል፡፡
በዚህም 144 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 157 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል።
በአፈጻጸሙ የእቅዱን 108 ነጥብ 5 በመቶ ማሳካት የተቻለ ሲሆን ÷ ገቢው ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ27 በመቶ ብልጫ እንዳለው አመልክተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ከታክስ በፊት 28 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ትርፍ መገኘቱን ነው የገለጹት፡፡
ተቋሙ ከ20 ዓመት በኋላ ነዳጅን ለመጀመሪያ ጊዜ ማጓጓዙን የጠቀሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው÷ ይህም ከአጠቃላይ ጭነቶች ውስጥ የ1 ነጥብ 7 በመቶ ድርሻ እንዳለው አብራርተዋል፡፡
በዓመቱ 2 ሚሊየን ቶን የአፈር ማዳበሪያ የተጓጓዘ ሲሆን ÷ ከዚህ ውስጥም 74 በመቶው በተሽከርካሪ እና 26 በመቶው ደግሞ በባቡር መጓጓዙን አስረድተዋል፡፡
ለኤክስፖርተሮች 34 ሺህ ኮንቴይነሮች መቅረባቸውን ገልጸው÷ እስከ 2030 የሀገሪቱን የኮንቴይነር አቅርቦት 100 ሺህ ለማድረስ መታቀዱን አመልክተዋል፡፡
በመሳፍንት እያዩ
Exit mobile version