👉 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ፍላጎትን በኃይል ለማሳካት፣ ሰዎችን በመግደልና አልጋ ሳይፀና በመገዳደል ስልጣን ለመያዝ የመሞከር አባዜ የባህላችን አንዱ አካል ሆኖ ቆይቷል፡፡
👉 ይህንንም በልጅ እያሱ፣ በጃንሆይ፣ በደርግ፣ በኢሕአዴግ እንዲሁም በቅርቡ በሰኔ 2010 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ ከተካሄደው ሙከራ ማየት ይቻላል፡፡
👉 የሰኔ 15ቱ ክስተት ከሌሎቹ የታሪክ አጋጣሚዎች ለየት የሚያደርገው በክልልና በከተማ ደረጃ ዝቅ ብሎ ለመፈጸም የተሞከረ መሆኑ ነው፡፡
👉 በክልል ደረጃ እንዲህ ያለውን ነገር ፈፅሞ አሳካለሁ ብሎ ማሰብ የስሁት ግምገማ ውጤት ነው፡፡
👉 በለውጡ ውስጥ ከፍተኛ ሚና ያላቸውን ቢቆዩ ብዙ ሊያበረክቱ የሚችሉ ሰዎችን ያሳጣ ክስተት ነው፤ ይህን የማስታውሰው የታሪካችንና የጠባሳችን አካል አድርጌ ነው
👉 በአንድ መንግሥት ወይም በአንድ ፓርቲ እቅድ የሚመራ ሳይሆን፣ እቅዱን ከተለያየ ምንጭ የሚወስድና እዚህም እዚያም የመሻት ፍላጎቱ የተቀላቀለበት ኃይል በጋራ በሚወያይበት ሒደት ውስጥ ጥፋት ሊያመጣ የሚችል ክስተት ተፈጥሯል፡፡
👉 አምባቸው መኮንን (ዶ/ር) ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ለለውጥ ከፍተኛ ጉጉት የነበራቸው፣ ሀሳብና እምነቶችን መቼና እንዴት እናሳካለን በሚለው ላይ ከአማራ ክልል እየመጡ በተደጋጋሚ በመምከርና በመወያየት ከፍተኛ ሚና የተጫወቱ መሪያችን ነበሩ፡፡
👉ከጀነራል ሰዓረ ጋር ከ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጀምሮ የቆየ ትውውቅ ነበረን ፤ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትና በለውጡ ዋዜማ በቅርበት ያገለገሉ ታማኝ ሰው ነበሩ፡፡
👉 በለውጡ ዋዜማ የመጀመሪያ እቅድ ወቅት የጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙንና የደህንነት ኃላፊውን በአንድ ጀምበር ለማንሳት በነበረው ውሳኔ ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የተሳተፉና ለለውጡ ሙሉ በሙሉ የታመኑ የሰራዊት መሪ ነበሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ባደረጉት ቆይታ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

