Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ዩክሬን ውስጥ በደረሰ የአውሮፕላን አደጋ የ22 ሰዎች ህይወት አለፈ

In this photo released by Kharkiv Regional State Administration, wreckage of an AN-26 military plane seen after it crashed in the town of Chuguyiv close to Kharkiv, Ukraine, late Friday, Sept. 25, 2020. A Ukrainian military plane carrying students at an aviation school crashed and burst into flames while landing, killing more than twenty people. Two other people on board were seriously injured and four people were missing. (Kharkiv Regional State Administration via AP)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዩክሬን በደረሰ የአውሮፕላን አደጋ የ22 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡
አንቶኖቭ-26 የተባለው የጦር አውሮፕላን የመከስከስ አደጋ ያጋጠመው በምስራቃዊ ዩክሬን ከተማ ለማረፍ በተቃረበበት ወቅት ነበር ተብሏል።
በአውሮፕላኑ 27 ሰዎች ተሳፍረው የነበረ ሲሆን 22ቱ መሞታቸው ሲረጋገጥ ሁለት ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ፡፡
ሶስቱ ሰዎች ደግሞ የጠፉ ሲሆን እነሱን ለማግኘት ፍለጋው ቀጥሏል ነው የተባለው፡፡
አውሮፕላኑ ከአገሪቱ አየር ኃይል አየር ማረፊያ መነሳቱ እና የልምምድ በረራ እንደነበረም ታውቋል፡፡
ከሟቾቹ መካከል አብዛኛዎቹ ሰልጣኝ አብራሪዎች መሆናቸውን የሃገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
የአደጋው መንስኤም በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ነው የተገለፀው፡፡
ምንጭ፡-ቢቢሲ
Exit mobile version