Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

መንግስት በመተከል ዞን የተከሰተውን አለመረጋጋት በአስቸኳይ መፍትሄ በመስጠት ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ተፈናቃይ ወገኖች ጠየቁ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከነበሩበት ቀየ ተፈናቅለው በጊዜያዊ መጠለያ በመኖራቸው ከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር መዳረጋቸውን በመተከል ዞን በተለያዩ የመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ዜጎች አስታወቁ፡፡

በመተከል ዞን በቡለን ወረዳ ከኩጅ ቀበሌ እና ሌሎች አካባቢዎች የተፈናቀሉት ወገኖች መንግስት መፍትሄ እንዲሰጣቸውም ጠይቀዋል።

እነዚህ ተጎጂ የማህበረሰብ ክፍሎች በመንግስት እና በተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች አማካኝነት የሰብዓዊ እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ገልጸው÷ ይህ በቂ ባለመሆኑ ወደ ነበሩበት ቀየ እንዲመለሱና የህግ የበላይነት የማረጋገጥ ስራው መጠናከር እንዲጠናከርም ነው የጠየቁት።

በቀጠናው አንጻራዊ ሰላም እስከሚሰፍን ድረስ የደረሱ ሰብሎችን ለመሰብሰብ በሚመለከተው አካል በኩል ጥበቃ እንዲደረግላቸው መጠየቃቸውንም ከመተከል ዞን ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በቡለን ወረዳ ብቻ ከ40 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ከቀያቸው ተፈናቅለው የሚገኙ ሲሆን÷ በአጠቃላይ በዞኑ ከ100 ሺህ በላይ ዜጎች በመጠለያ ጣቢያዎች እንደሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version