Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ እና እስራኤል የኮቪድ19 ክትባትን በጋራ ማምረት በሚችሉበት አግባብ ላይ ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና እስራኤል የኮቪድ19 ክትባትን በጋራ ማምረት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በኢትዮጵያ ከእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱ እና ምክትል አምባሳደር ኦር ዳንኤሊ ጋር በጤናው ዘርፍ በጋር መስራት በሚቻልባቸው አግባቦች ላይ ተወያይተዋል፡፡

በዚህ ወቅትም ሃገራቱ በጋራ የኮቪድ19 ክትባትን ማምረት በሚችሉበት አግባብ ላይ፣ በአቅም ግንባታ፣ በጤናው ዘርፍ ኢንቨስትመንት እና በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ማሳደግ በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version