Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የፌደሬሽን ምክር ቤትን ስልጣንና ተግባር ለመዘርዘር ተሻሽሎ የወጣውን አዋጅ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደሬሽን ምክር ቤትን ስልጣንና ተግባር ለመዘርዘር ተሻሽሎ የወጣውን አዋጅ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አጸደቀ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ ልዩ ስብሰባውን አካሂዷል።
በዚህም የፌደሬሽን ምክር ቤትን ስልጣንና ተግባርን ለመዘርዘር ተሻሽሎ የወጣውን አዋጅ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ በዓለም አቀፉ የልማት ማህበርና በኢትዮጵያ መካከል ለተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እንዲውል የተፈረሙ አራት የብድር ስምምነቶችን ማጽደቁን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ምክር ቤቱ በዛሬ ስብሰባው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የመንገድ ደህንነት ቻርተርና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር የተስማማችባቸውን ሁለት የመንገድ ደህንነት ቻርተሮችንም አፅድቋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version