አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ የተመሰረተው ጨፌ ኦሮሚያ እያካሄደ ባለው የመጀመሪያ ጉባኤው አቶ ሽመልስ አብዲሳን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾሟል፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው የተሾሙት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው፥ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮችና የካቢኔ አባላት ሆነው ሊያገለግሉ የሚችሉ ተሿሚዎችን ጨፌው ያፀድቅላቸው ዘንድ የአባላቱን ማንነት በማስተዋወቅ ላይ ናቸው።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!