Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የምክር ቤቱን አሰራር የሚያሻሽሉ ዲጂታል መተግበሪያዎች ይፋ ተደረጉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሰራርን የሚያሻሽሉ አራት ዲጂታል መተግበሪያዎች ይፋ ተደርገዋል።
መተግበሪያዎቹ መረጃን በቀላሉ ለመለዋወጥ የሚያስችሉ እና የተደራሽነት ችግርን የሚቀርፉ ናቸው ተብሏል።
መተግበሪያዎቹ ከ1934 ዓ.ም ጀምሮ በምክር ቤቱ የሚገኙ ቃለ ጉባኤዎች እና ሰነዶችን በቀላሉ ለማግኘት ያስችላል ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ተናግረዋል፡፡
መረጃን ለማግኘት ይወስድ የነበረውን ጊዜ እና ገንዘብ የሚቆጥቡ፣ ህዝብ እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ግንኙነትም የሚያጠናክሩ መሆናቸውንም አፈ ጉባኤው ገልጸዋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version