Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለዊሊያም ሩቶ በዓለ ሲመት ናይሮቢ ገቡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲሱ የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በዓለ ሲመት ለመታደም ኬንያ፣ ናይሮቢ ገቡ።

ዊሊያም ሩቶ በቅርቡ በሀገሪቱ በተካሄደ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የኬንያ አምስተኛ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ይታወቃል።

በበዓለ ሲመቱ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች እንደሚታደሙ ይጠበቃል ።

 

 

ዊልያም ሩቶ በካሳራኒ ስታዲየም እየተካሄደ በሚገኘው የበዓለ ሲመታቸው ሥነ ሥርዓት ላይ ቃለ መሓላ ይፈጽማሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በዓልአዛር ታደለ

Exit mobile version