Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ችግር በበርካታ አካባቢዎች የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ችግር የኃይል መቋረጥ ማጋጠሙን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጸው ፥ ጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ያጋጠመውን ችግር ወደነበረበት ለመመለስ እየተሰራ ነው፡፡

ችግሩ እንደተቀረፈም የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎቱ ወደነበረበት እንደሚመለስ አስታውቋል፡፡

Exit mobile version