አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫነት የሚውሉ ሁሉም የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች በቂ ውኃ መያዛቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን እንዳሉት÷ ጊቤ 3፣ ገናሌ ዳዋ እና ጊቤ 1 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ኃይል ማመንጨት የሚያስችላቸውን በቂ ውኃ ይዘዋል።
እንደ ጊቤ 2፣ አዋሽ 2 እና 3 ያሉና ሌሎች የኃይል ማመንጫዎች ኃይል ለማመንጨት የሚያስችላቸው በቂ ውኃ እየገባ መሆኑን ነው የጠቆሙት፡፡
በያዝነው የክረምት ወቅት ውኃ ያልያዘ የኃይል ማመንጫ አለመኖሩንም አስረድተዋል።
በዮሐንስ ደርበው
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!