Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ከዩኤንዲፒ ረዳት ዋና ፀሃፊና የአፍሪካ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴከተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ) ረዳት ዋና ፀሃፊ እና የአፍሪካ ዳይሬክተር አሁና ኤዚያኮንዋ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የተለያዩ የልማት ጉዳዮች ላይ መምከራቸው ተገልጿል፡፡

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ÷ዩኤንዲፒ በኢትዮጵ ላከናወናቸውና እየሠራቸው ላሉ ተግባራት ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

በሌላ በኩል ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ሴቶችን በግብርና ማብቃት ላይ ባተኮረ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር÷“በገጠር የሚገኙ ሴቶችን ማብቃት የፍትሕ፣ የእኩልነትና የሰብዓዊ መብት ጥያቄ ነው” ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ሴቶችን በግብርና ዘርፍ ለማብቃት ጥረት ማደረግ እንደሚገባ ጠቁመው÷በዚህም ለሁሉም ሴቶች የመልማት ተስፋ ያለበትና አፍሪካ ለመጪው ትውልድ የመልካም ዕድል ብርሃን የምትፈነጥቅበት ጊዜ መገንባት እንችላለን ብለዋል፡፡

Exit mobile version