Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ሕዳሴ ግድብ የመደመር ዕሳቤ የታተመበት ፕሮጀክት ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሕዳሴ ግድብ ከጫፍ እስከ ጫፍ በሁሉም የኢትዮጵያ ማዕዘናት የኢትዮጵያ ልጆችን ለልማት ያስተባበረና የመደመር ዕሳቤ የታተመበት ፕሮጀክት ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ተራሮች በሸለቆ እና በሜዳ ገሰግሶ እንደሚገናኘው ታላቁ ዓባይ የብዝሃነት ቤት በሆነችው ድሬዳዋ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ ዛሬ የድጋፍ ሰልፍ ተደርጓል ብለዋል።
በሕዳሴ ግድብ ያየናቸው በፈተናዎች መካከል እንደ አለት ጸንቶ በመቆም ማሸነፍ በድሬዳዋ ያሉ የልማት አቅሞችን ለሀገር ልማት ለማዋል ብርታት ይፈጥራል ነው ያሉት።
ድሬዳዋ የሰላም እና የፍቅር ብቻ ሳይሆን ለልማት እና ለውጥ መበርታትም መገለጫዋ ነው ሲሉም አመልክተዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version