Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ብሔራዊ ባንክ በአዲሱ የባንክ አዋጅ መሰረት ለስታንዳርድ ባንክ አዲስ ፈቃድ ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብሔራዊ ባንክ በተሻሻለው የባንክ ንግድ አዋጅ መሠረት ለስታንዳርድ ባንክ የኢትዮጵያ ተወካይ ቢሮ አዲስ ፈቃድ ሰጥቷል።

ፈቃዱ የተሰጠው የውጭ ባንክ ተወካይ ቢሮዎች ፈቃድና ቁጥጥር በቀጥታ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ስር እንዲሆኑ በተደነገገው የተሻሻለው ሕግ መሰረት ነው።

በዚህም ባንኩ የተወካይ ቢሮዎች በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የተሰጣቸውን ፈቃድ በማደስ አዲስ ፍቃድ የመስጠት ስራ ጀምሯል።

በኢትዮጵያ ውስጥ ለረጅም ጊዜ በውክልና ቢሮው በኩል የሚንቀሳቀሰው ስታንዳርድ ባንክ በአዲሱ የቁጥጥር ማዕቀፍ መሰረት ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ያገኘ የመጀመሪያው የውጭ ተቋም መሆን ችሏል።

ፈቃድ የሚሰጣቸው የውክልና ቢሮዎቹ ለውጭ ባንኮች የግንኙነትና የንግድ መረጃ ማዕከላት በመሆን የገበያ ጥናቶችን በማካሄድ፣ የንግድ ግንኙነቶችን በመገንባትና በማስተዋወቅ ያገለግላሉ።

እነዚህ የውክልና ቢሮዎች በባንክ አገልግሎቶችም ሆነ በገንዘብ ዝውውር አገልግሎት ውስጥ የሚሳተፉ አለመሆናቸውን ባንኩ ለፋና ዲጅታል በላከው መረጃ አመላክቷል።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version