Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የሸበሌ ሪዞርት የዘመናዊ ሥነ ሕንጻ ጥበብ ከሶማሌ ክልል ባሕላዊ እሴት ጋር አቀናጅቶ የያዘ የታሪክ ማኅደር ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

default

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሸበሌ ሪዞርት መዝናኛ ስፍራ ብቻ ሳይሆን የዘመናዊ ሥነ ሕንጻ ጥበብ ከሶማሌ ክልል ባሕላዊ እሴት ጋር አቀናጅቶ የያዘ የታሪክ ማኅደር ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ከ’ገበታ ለትውልድ’ ዐቢይ ፕሮጀክቶች መካከል ሁለተኛውን እና በ385 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውን የሸበሌ ሪዞርትን መርቀን ለአገልግሎት አብቅተናል ብለዋል።

ሪዞርቱ መዝናኛ ስፍራ ብቻ ሳይሆን የዘመናዊ ሥነ ሕንጻ ጥበብን ከሶማሌ ክልል ባሕላዊ እሴት ጋር አቀናጅቶ የያዘ የታሪክ ማኅደር መሆኑንም ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የገባነውን ቃል በተግባር ያረጋገጠ የምስራቁ የሀገራችን ክፍል ትልቅ ሥራ ነው ሲሉም አመልክተዋል።

በክልሉ የሚገኘው እጅግ ሰፊ እና ማራኪ ተፈጥሯዊ ጸጋ በመደመር ዕሴትና ትብብር ወደ ልማት ሲለወጥ ኢትዮጵያ የምታልም ብቻ ሳትሆን ህልሟን ወደ እውነት የምትቀይር እና የምትኖር ሀገር መሆኗን በተግባር አሳይቷልም ነው ያሉት በመልዕክታቸው።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Telegram https://fanamc.com/amharic/

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version