Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ም/ጠ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ ከዛሬ ጀምሮ በህንድ ጉብኝት ያደርጋሉ

Ethiopia's Deputy Prime Minister Demeke Mekonnen watches a live transmission of the Ethiopian ETRSS-1 Satellite launch into space at the Entoto Observatory and Research Center on the outskirts of Addis Ababa, Ethiopia December 20, 2019. REUTERS/Tiksa Negeri

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከዛሬ ጀምሮ በህንድ ጉብኝት ያደርጋሉ።

አቶ ደመቀ እስከ መጪው አርብ በህንድ በሚኖራቸው ቆይታ በተለያዩ ስነ ስርዓቶች ላይ እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

በዚህም በህንድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያስገነባውን ህንፃ እና የዲፕላማቶች መኖሪያ ከህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሱብራህማንያም ጀሽንከር ጋር በመሆን በመጪው ሀሙስ ይመርቃሉ ተብሏል።

በተመሳሳይ አቶ ደመቀ ከህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሱብራህማንያም ጀሽንከር ጋር በኢትዮጵያ እና ህንድ የሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ እንደሚወያዩ ነው የተነገረው።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version