አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም መክፈቻ መርሐ- ግብር ላይ ንግግር አድርገዋል፡፡
በንግግራቸውም÷ የቻይና-አፍሪካን ግንኙነት ጥንተ መሰረት እና እድገት አውስተዋል፡፡
በቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም የመሰረተ ልማት ክንውን በአፍሪካ አህጉር የተጣለውን ጠንካራ የትብብር መሰረትም አንስተዋል::
በማደግ ላይ ያለውን የአፍሪካን ተፅእኖ የመፍጠር አቅም አፅንዖት የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ በባለብዙ ወገን መድረኮች አካታችነትን ማረጋገጥ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል::
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!