Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም ላይ ንግግር አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም መክፈቻ መርሐ- ግብር ላይ ንግግር አድርገዋል፡፡

በንግግራቸውም÷ የቻይና-አፍሪካን ግንኙነት ጥንተ መሰረት እና እድገት አውስተዋል፡፡

በቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም የመሰረተ ልማት ክንውን በአፍሪካ አህጉር የተጣለውን ጠንካራ የትብብር መሰረትም  አንስተዋል::

በማደግ ላይ ያለውን የአፍሪካን ተፅእኖ የመፍጠር አቅም አፅንዖት የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ በባለብዙ ወገን መድረኮች አካታችነትን ማረጋገጥ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል::

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.