ለድርቅ እና ግጭት ተጋላጭ የሆኑ አካላትን በጥናት በመለየት ድጋፍ እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
ለ500 አባወራዎች ለእያንዳንዳቸው 4 ሺህ ብር ለማስተላለፍ የሚያስችል የተጠቃሚዎች የባንክ ሂሳብ ቁጥር እየተከፈተላቸው መሆኑን የገለጹት አቶ ጌታቸው÷ እስካሁን 300 የሚሆኑ ሰዎች የባንክ ሂሳብ የከተከፈተላቸው ሲሆን በዚህ ሳምንት ለተቀሩት በመክፈት ገንዘቡ ይተላለፍላቸዋል ነው ያሉት፡፡
ድጋፉ በገንዘብ መሆኑና በቀጥታ በተጎጂዎቹ የባንክ ሂሳብ ላይ ገቢ መደረጉ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረትና የህብረተሰቡን የቁጠባ ባህል ለማሳደግ ሁነኛ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል፡፡
በማኅበሩ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ጀማል አባቦራ÷ በክልሉ ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የዕለት ድጋፍና በቋሚነት እንዲቋቋሙ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው÷ በባሌ ዞን ጎሮ ወረዳ ከ17 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ የሚገኘው ዘመናዊ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት የዚሁ አካል መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የድርቅ ተጎጂዎቹ በበኩላቸው÷ የባንክ ሂሳብ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እየተከፈተላቸው መሆኑን ገልጸው÷ በቀጣይ ከድርቁ አገግመው የተረጋጋ ኑሮ ለመምራት እንዲችሉ መንግስት የምርጥ ዘርና ሌሎች ዘላቂ ድጋፎችን እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡