Fana: At a Speed of Life!

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአፍሪካ የሚያደርጉትን ጉብኝት በደቡብ አፍሪካ ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በአፍሪካ የሚያደርጉትን ጉብኝት ደቡብ አፍሪካ በመግባት ጀምረዋል፡፡

ጉብኝቱ አንቶኒ ብሊንከን ሩሲያ በአፍሪካ ያላትን ተፅዕኖ ለማሳደግ የምታደርገውን ጥረት ለመመከት እንደሆነ ተገልጿል፡፡

በዚህም የመጀመሪያ የአፍሪካ ጉብኝታቸውን ደቡብ አፍሪካ በመግባት ጀምረዋል፡፡

ባለፈው ወር የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት የአፍሪካ ሀገራትን መጎብኘታቸው ይታወሳል፡፡

ከፕሪቶሪያ በኋላ ብሊንከን ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሩዋንዳን ይጎበኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ቢቢሲ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.