Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮ ቴሌኮም በ2016 በጀት አመት የደንበኞቹን ቁጥር 78 ሚሊየን ለማድረስ አቅዷል

 

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮ ቴሌኮም በ2016 በጀት አመት የደንበኞቹን ቁጥር 78 ሚሊየን ለማድረስ ማቀዱን አስታውቋል።

የቴሌብር ደንበኞች ቁጥሩንም ወደ 41 ነጥብ 1 ሚሊየን እንደሚያሳድግ ነው ያስታወቀው።

ኩባንያው የቀጣዩ አመት እቅዱን ይፋ አድርጓል።

ኩባንያው መሰረተ ልማትን በማስፋፋት ተደራሽነቱን ለማሳደግ ማቀዱን ያስታወቀ ሲሆን÷ ገቢውን ለማሳደግ የሚያስችሉ አዳዲስ አሰራሮችንም እንደሚያስተዋውቅ ገልጿል።

የሞባይል ኔትዎርኮችን ማስፋፋት፣ የተቋማት አገልግሎት በቴክኖሎጂ ማገዝም በትኩረት እንደሚሰራበት ነው የተመላከተው።

ኢትዮ ቴሎኮም በመሰረታዊ የቴሌኮም አገልግሎት በአዳዲስ አገልግሎቶች በአጠቃላይ በመጪው አመት 90 ነጥብ 5 ቢሊየን ለማግኘት ማቀዱንም ገልጿል።

በትዕግስት ብርሃኔ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.