Fana: At a Speed of Life!

የፀጥታ መዋቅሩ ከሠራዊቱ ጋር በመቀናጀት ሠላም የማረጋገጥ ሥራ እያከናወነ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐይቅ ከተማ የፀጥታ መዋቅር ከሠራዊቱ ጎን በመሰለፍ የሚሠጠውን ግዳጅ መፈፀም በሚያስችለው ቁመና ላይ መሆኑን በተግባር አስመስክሯል ሲሉ ብርጋዲየር ጄኔራል ዘውዱ ሠጥአርጌ ገለጹ፡፡

በቀጣናው ሕገ-ወጥ ቡድኖችን ለማፅዳት ሠራዊቱ በሚያከናውነው ተልዕኮ የከተማዋ የፖሊስ አባላትና ሚሊሻ በቁርጠኝነት በመሠለፍ በተካሄደው ኦፕሬሽን ሕገ- ወጥ ቡድኑ ስጋት ወደማይሆንበት ደረጃ ደርሷል ብለዋል ብርጋዲየር ጄኔራል ዘውዱ፡፡

ሠራዊቱ ከሐይቅ ከተማ የፀጥታ መዋቅር ጋር በመተባበር በሕገ-ወጥ ቡድኑ እጅ የነበሩ የጦር መሣሪያዎችን ይዟል ማለታቸውን ከመከላከያ ሠራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

የሕገ- ወጥ ቡድኑን አባላት ከማሕበረሰቡ ነጥሎ ለማውጣት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.