Fana: At a Speed of Life!

የመከላከያ ሚኒስቴርና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በጋራ ለመስራት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመከላከያ ሚኒስቴር እና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በማሪታይም ዘርፍና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

ስምምነቱን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የመከላከያ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ በመረጃ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ እንዲሁም በዓለም አቀፍ የውሃ ህግጋት ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ነውመባሉን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ሚኒስትሮቹ በሰጡት መግለጫ ስምምነቱን በአግባቡ ለመተግበር አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.