Fana: At a Speed of Life!

ኮይካ ኢትዮጵያ በዲጂታል ልማት እያደረገች ያለችውን ጥረት እንደሚደግፍ ገለፀ

 

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ኢትዮጵያ በዲጂታል ልማት እያከናወነች ያለውን ጥረት እንደሚደግፍ አስታወቀ።

በኢትዮጵያ የኮይካ ዳይሬክተር ሀን ዲዮግ ቾ ÷ በኢትዮጵያ የአምራችና የጤናውን ዘርፍ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና አካታች ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፉ ገልፀዋል።

ኮይካ በዲጂታል ዘርፉም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው÷ የኤሌክትሮኒክስ አገልግሎት አሰጣጥን እየደገፈ መሆኑን አንስተዋል።

በአይሲቲ ዘርፍ ያሉ ስታርትአፖችን በአቅም ግንባታና በገንዘብ እየደገፉ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ባለንበት ዘመን ኢኮኖሚን ለማሳደግና ማህበረሰብን ለማበልፀግ ዲጂታል እውቀት የግድ መሆኑን ጠቅሰው ÷ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ መንግስት ዲጂታላይዜሽን ላይ እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ እንደሆነ ገልጸዋል።

በእያንዳንዱ የልማት ትብብሮች የተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከናወኑ መሆናቸውንና ለዚህም 150 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በጀት እንደተመደበ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.