ኔዘርላንድስ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር እንደምታጠናክር ገለጸች
አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኔዘርላንድስ በተለያዩ ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከረ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጻለች፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከኔዘርላንድስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ስቲጅን ጃንሰን ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በሀገራቱ የሁለትዮሽ ትብብር እና በቀጣናዊ ትስስር ጉዳዮች ላይ በትኩረት መክረዋል፡፡
ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)÷በቅርቡ በኢትዮጵያ የተከሄደውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሒደት አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል፡፡
ስቲጅን ጃንሰን በበኩላቸው÷የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጠቃላይ ለውጥ ማድነቃቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
ኔዘርላንድስ ከኢትዮጵያ ጋር በኢንቨስትመንት፣ በልማት፣ በንግድና ሌሎች ዘርፎች ያላትን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗንም አረጋግጠዋል፡፡