Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ የዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት ስልጠና ማዕከል ሆና ተመረጠች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የስልጠና ማዕከል ሆና መመረጧን የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

ኢንስቲትዩቱ የአፍሪካ አህጉር የስልጠና ማዕከልን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ሲያደርግ የነበረው ጥረት በዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት ተቀባይነት ማግኘቱ ተገልጿል።

ስኬቱ ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ሁነት እንድታስተናግድ እንደሚረዳ መገለጹን የኢትዮጵያ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት መረጃ ያመላክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.