334 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 334 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከየካቲት 14 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ነው 248 ሚሊየን ብር የገቢ እና 86 ሚሊየን ብር የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎች የያዘው፡፡
ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ ጥራጥሬ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች ፣ መድኃኒት፣ የቁም እንስሳት እና የወጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡