Fana: At a Speed of Life!

የጥበብ ባለሙያዎች በችግር ጊዜ የሀገርን ጥቅም ሊያስቀድሙ ይገባል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

የጥበብ ባለሙያዎች በችግር ጊዜ የሀገርን ጥቅም ሊያስቀድሙ ይገባል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በችግር ጊዜ ከግል ጥቅም ይልቅ ለሀገር ጥቅም የተሳተፉ የጥበብ ባለሙያዎች ስማቸው ምንጊዜም በወርቅ አሻራ ተጽፎ ይኖራል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከመላው ኢትዮጵያ ከተወጣጡ የጥበቡ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ባደረጉት ውይይት÷ የኪነ ጥብብ ባለሙያዎች በየትኛውም ሁኔታ ለሀገር ጥቅም መከበር ቁርጠኛ መሆን አለባቸው ብለዋል፡፡

ባለሙያዎች በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ሙዚቃ፣ ፊልም፣ ኮንሰርትና ሌሎች የጥበብ ክዋኔዎችን በመስራት ለማሕበረሰቡ ማሳየት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡

ኢትዮጵየ በኢኮኖሚ ፈጣን እድገት እያሳየች መሆኑን አንስተው ÷ የኪነ ጥበብ ባለሙዎችም የኢኮኖሚ እድገቱን የዋጀ ዝግጁነት ሊኖራቸው ይገባል ነው ያሉት፡፡

በችግር ጊዜ ከግል ጥቅም ይልቅ ለሀገር ጥቅም የተሳተፉ የጥበብ ባለሙያዎች ስማቸው ምንጊዜም በወርቅ አሻራ ተጽፎ እንደሚኖር አንስተዋል፡፡

በችግር ጊዜ ሀገራቸውን ለከዱት ይቅርታ አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ÷ ኢትዮጵያን ክዶ ከመጣው ጋር በጥቅም ተሳስሮ ሃብታም ከመሆን ቢቀር ይሻላል ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ኪነ ጥበብ ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ብልጽግና የማይተካ ሚና እንዳለው ገልጸው ÷ ለሀገር አንድነትና ግንባታ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጻፏቸው የመደመር እና የመደመር ትውልድ መጽሃፎች ላይ ኪነ ጥበብ ለአንድ ሀገር እድገት ያለው ድርሻ በግልጽ መቀመጡን አስታውሰዋል።

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.