5 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር በሬሚታንስ ወደ ሀገር ተላከ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከውጭ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ በሬሚታንስ 5 ነጥብ1 ቢሊየን ዶላር ተልኳል አለ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት፡፡
የአገልግሎቱ የፕላን ክፍል ሃላፊ ወንድወሰን ተረፈ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ የዳያስፖራውን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
በበጀት ዓመቱ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ ዳያስፖራው ወደ ሀገር የሚልከው ሬሚታንስ እንዲጨምር ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡
ዳያስፖራው የውጭ ምንዛሬ አካውንት እንዲከፍት መደረጉን ጠቁመው÷ በዚህም 18 ሺህ 889 አካውንት ማስከፈት ተችሏል ነው ያሉት፡፡
በተከፈተው አካውንትም 25 ነጥብ 2 ሚሊየን ዶላር መቆጠቡን ያነሱት ሃላፊው ÷ ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር ከፍተኛ እድገት ማሳየቱን አስረድተዋል፡፡
በሌላ በኩል ከዳያስፖራ የሚገኘውን ሬሚታንስ ለማሳደግ በተደረገው ድጋፍና ክትትል 5 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር በሬሚታንስ ወደ ሀገር መላኩን ጠቅሰዋል፡፡
ለሬሚታንስ መጨመር በኢትዮጵያ የተደረገው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
በመላኩ ገድፍ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!