Fana: At a Speed of Life!

የአካባቢውን ታሪክና የተፈጥሮ ጸጋ ያጣመረው ሀላላ ኬላ ሪዞርት…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የሀላላ ኬላ ሪዞርትን ጎብኝተዋል።

ባለሙያዎቹ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ከተወያዩ በኋላ ነው ዳውሮ ዞን የሚገኘውን ሀላላ ኬላ የጎበኙት፡፡

የገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክት አካል የሆነው ሀላላ ኬላ ሪዞርት የአካባቢውን ታሪክ እና የተፈጥሮ ጸጋ አጣምሮ የያዘ ውብ ስፍራ ነው።

ባለሙያዎቹ የጊቤ ሦስት የኃይል ማመንጫ የፈጠረውን ሰው ሰራሽ ሃይቅ የመስህብ ሥፍራ እና የንጉስ ሀላላ ካብንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡

ሀላላ ኬላ ሪዞርት ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ የመዝናኛ ሥፍራዎች፣ ባሕላዊ እና ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ሙዚዬም እንዲሁም መሰብሰቢያ አዳራሾችን አካትቶ ይዟል፡፡

ሪዞርቱ የዳውሮ ሕዝብ ጥንታዊ የካባ አሰራር መልክን የገለጠ እና የሀገርን ጸጋ ወደ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የቀየረ መሆኑን የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ እድል በመፍጠር ረገድ በሰው ሰራሽ ሐይቁ በአሳ ማጥመድ እና ጀልባ ሽርሽር ተደራጅተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻሉ የሚበረታታ ነው ብለዋል።

መንግስት በብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ለቱሪዝም ዘርፍ የሰጠው ትኩረት ውጤታማነት ማሳያ አንዱ ምልክት ሀላላ ኬላ እንደሆነም ባለሙያዎቹ አብራርተዋል።

በኃይለኢየሱስ መኮንን

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.