Fana: At a Speed of Life!

ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓት የፍትሕ ተደራሽነትን እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓት የፍትሕ ተደራሽነትን እያሳደገ ነው አሉ የፍትሕ ሚኒስትር ሀና አርአያስላሴ።

በኢትዮጵያ የሕግ ሥርዓት ውስጥ ባሕላዊ የግጭት መፍቻ ዘዴን ለማካተት መወሰድ በሚገባቸው ርምጃዎች ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡

ወ/ሮ ሃና አርአያስላሴ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት ግጭቶች በባሕላዊ የፍትሕ ሥርዓት ሲፈቱ ቆይተዋል።

ሕብረተሰቡ ለበርካታ ዘመናት ሲጠቀምባቸው የቆዩ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች የሕግ ዕውቅና እንዲያገኙ፣ እንዲበረታቱና እንዲስፉፉ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

መንግስት በፍትሕ ትራንስፎርሜሽን እቅዱ የማሕበረሰብ ፍትሕ ተቋማት እንዲስፋፉ በማድረግ እውቅና እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓት የፍትሕ ተደራሽነትን እያሳደገ መሆኑን አንስተው÷ በዚህም በማሕበረሰቡ መካከል የሚከሰቱ ግጭቶች እየተፈቱበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በቀጣይ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶችን ማጠናከር የሚያስችሉ ሥራዎች በትኩረት ይሰራሉ ማለታቸውንም ኢዜአ ነው የዘገበው፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.