Fana: At a Speed of Life!

በምክር ቤቱ የጸደቁ ፕሮጀክቶችን ለመጨረስ ወደ 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ያስፈልጋል – አቶ አህመድ ሺዴ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በ2018 ረቂቅ በጀት ላይ ከምክር ቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም የልማት ጥያቄዎች ብዙ በመሆናቸው ሁሉንም ጥያቄዎች ለመመለስ አቅም እንደሚጠይቅ አንስተው÷ በ2018 በጀት ዓመት አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ይልቅ የተጀመሩትን ለማጠናቀቅ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።

አሁን ባለው ሁኔታ ምክር ቤቱ ያጸደቃቸውን ፕሮጀክቶች ለመጨረስ ወደ 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ያስፈልጋልም ነው ያሉት።

በምክር ቤቱ ጸድቀው ጨረታ ያልወጣላቸው ፕሮጀክቶችን ለማከናወንም ወደ 100 ቢሊየን ብር እንደሚጠይቅ አንስተዋል።

አሁን ላይ በኢኮኖሚ ሪፎርሙ ምክንያት በመንግስት ላይ የተፈጠረው የወጪ ጫና በታሪክ ትልቁ እንደሆነ አመላክተው÷ በ2018 በጀት ዓመት የገቢ ምንጩን የሚያሳድግበት ስራ ይሰራል ብለዋል።

የመንግስት የ2018 ረቂቅ በጀት 1 ነጥብ 93 ትሪሊየን ብር ሆኖ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ይታወሳል።

በታሪኩ ለገሰ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.