በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተከሰተው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ሥር ዋለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላይ የተከሰተውን የእሳት አደጋ መቆጣጠር ተችሏል።
አደጋው ከቀኑ 8:00 ሰዓት አካባቢ የተከሰተው የእሳት አደጋ መንስኤው እየተጣራ ይገኛል።
እሳቱን ለመቆጣጠር ሕብረተሰቡ እና የጸጥታ አካላት የተቀናጀ ብርቱ ጥረት ያደረጉ ሲሆን፤ በአደጋው የሆስፒታሉ ቀዶ ሕክምና፣ የውስጥ ደዌ ሕክምና እና ተመላላሽ ሕክምና ክፍሎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተጠቁሟል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀድሞ ስሙ ኦቶና ሆስፒታል አንጋፋ እና ከወላይታ ዞን ውጪ በአጎራባች ዞኖች ላሉ ነዋሪዎች ጭምር አገልግሎት የሚሰጥ ሆስፒታል ነው።
በማቱሳላ ማቴዎስ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!