በመዲናዋ የኢንተርፕራይዞችን ውጤታማነት የሚጨምሩ ስራዎች ተከናውነዋል
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 22፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢንተርፕራይዞችን ውጤታማነት የሚጨምሩ ስራዎች ተከናውነዋል አለ የከተማ አስተዳደሩ ስራና ክህሎት ቢሮ።
በቢሮው የስራ ስምሪት አገልግሎት ዳይሬክተር ሰብሀዲን ሱልጣን ለፋና ሚዳያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷ ለኢንተርፕራይዞች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በተሰራው ስራ በበጀት ዓመቱ ለ2 ሺህ 250 ኢንተርፕራይዞች መስሪያ ቦታ ተሰጥቷቸዋል፡፡
የብድር አቅርቦትን በማስፋት ከ3 ቢሊየን ብር በላይ ለ7 ሺህ 500 ኢንተርፕራይዞች ብድር መሰጠቱን አንስተው÷ ከ12 ሺህ በላይ አዳዲስ ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት ወደ ሥራ ማስገባት ተችሏል ነው ያሉት።
አሁን ላይ በከተማዋ የሥራ ዕድልን በተለያዩ ዘርፎች በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል፡፡
በከተማ ግብርና፣ ኢንዱስትሪ እና አገልግሎት ዘርፎች ላይ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
በሰለሞን ይታየው
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!