ኢትዮ ጅቡቲ ባቡር የአፍሪካ የኢኮኖሚ ትብብር ተምሳሌት ነው – ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮ ጅቡቲ ባቡር የአፍሪካ የኢኮኖሚ ትብብር ተምሳሌት ነው አሉ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)።
“የባቡር መሠረተ ልማት ለንግድና ቀጣናዊ ትስስር” በሚል ሐሳብ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
በውይይቱ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ፣ የብሄራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ፣ የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ታከለ ኡማ፣ የጅቡቲ ተወካዮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ኢትዮ ጅቡቲ ባቡር የአፍሪካ የኢኮኖሚ ትብብር ተምሳሌት መሆኑን ገልጸው÷ በባቡር ትራንስፖርት ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ጋር ለማስተሳሰር እየተሰራ ነው ብለዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ በበኩላቸው÷ የጅቡቲ ወደብ የጭነት ማንሳት አቅምን የሚያሳድግ መሆኑን አንስተው÷ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣናን ያሳልጣልም ነው ያሉት።
የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ታከለ ኡማ የተቋሙን አሰራር ዘመናዊ የማድረግ ሥራዎች በመሰራታቸው ከዘርፋ መገኘት የሚገባንን ጥቅም እያገኘን ነው ብለዋል።
በቅድስት አባተ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!