በክልሉ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ450 ሺህ በላይ ሰዎች ተጠቃሚ ሆነዋል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጋምቤላ ክልል ሴቶች እና ማሕበራዊ ጉዳዮች ቢሮ በወጣቶች በተከናወነ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ450 ሺህ በላይ ሰዎች ተጠቃሚ ሆነዋል አለ።
በቢሮው የወጣቶች አደረጃጀት እና ተሳትፎ ዳይሬክተር አቶ ደመላሽ ያደቴ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት፤ በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ወጣቶች ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ ነው።
በክልሉ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ70 ሺህ በላይ ወጣቶችን ለማሳተፍ መታቀዱን ገልጸው፤ አረንጓዴ ዐሻራ፣ ሰላምና ጸጥታን ጨምሮ በ14 የስራ ዘርፎች ወጣቱን በማሳተፍ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል።
በዚህም እስካሁን 30 ሺህ የሚጠጉ ወጣቶች ተሳትፎ በማድረግ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት አገልግሎት መስጠታቸውን ጠቅሰው፤ በአገልግሎቱ ከ450 ሺህ በላይ የሚሆኑ የማሕበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ሆነዋል ነው ያሉት።
በክልሉ እየተከናወነ የሚገኘው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንደሚቀጥል ገልጸው፤ ወጣቶች ያላቸውን ተሳትፎ እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።
በዮናስ ጌትነት
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!