Fana: At a Speed of Life!

በባሕርዳር የመስቀል ደመራ በዓልን አስመልክቶ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በባሕርዳር ከተማ የመስቀል ደመራ በዓልን አስመልክቶ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል።

የፅዳት ዘመቻው በአካባቢ ጥበቃ ጽዳትና ውበት ጽ/ቤት አስተባባሪነት የተካሄደ ነው።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የባሕርዳር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ተሻገር አዳሙ እንዳሉት፤ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የ2018 ዓ.ም የመስቀል በዓል በማስመልከት የፅዳት ዘመቻ ንቅናቄ ተካሂዷል።

የከተማዋን ፅዳትና ውበት በመጠበቅ ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ህብረተሰቡን በማሳተፍ ተጠናክረው እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.