Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ቡና ነገሌ አርሲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሁለተኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ነገሌ አርሲን 2 ለ1 አሸንፏል፡፡

የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች አቡበከር አዳሙ እና በፍቃዱ አለማየሁ አስቆጥረዋል፡፡

ነገሌ አርሲን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ገ/መስቀል ዱባለ ከመረብ አሳርፏል፡፡

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከፋሲል ከነማ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከአዳማ ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚጫወቱ ሲሆን÷ ወላይታ ድቻ ከድሬዳዋ  ከተማ  ደግሞ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የሚጫወቱ ይሆናል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.