Fana: At a Speed of Life!

የትግራይ ሕዝብ ሕወሓት በሰሜን ዕዝ ላይ በፈጸመው ጥቃት አዝኗል – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የትግራይ ክልል ሕዝብ ሕወሓት በሰሜን ዕዝ ላይ በፈጸመው ጥቃት አዝኗል አሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ።

በሀገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት የተፈፀመበት 5ኛ ዓመት “እንዳይደገም ፤ መቼም አንረሳውም” በሚል መሪ ሃሳብ በዛሬው ዕለት ታስቦ ውሏል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በመርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት÷ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ሕወሓት በሰሜን ዕዝ ላይ በፈፀመው ጥቃት የክልሉ ሕዝብ አዝኗል ነው ያሉት።

የመከላከያ ሰራዊት በሕግ ማስከበሩ ወቅት የትግራይ ሕዝብ ትንኮስ አለማድረጉንና በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈፀመውን ክህደትም እንደማይቀበል አንስተዋል፡፡

በወቅቱ የደረሰው ጥቃትም መካድ የለመደ የአንድ ከሃዲ ቡድን ስራ ነው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ÷ ይህንንም ከጀመረ 50 ዓመቱ ነው ብለዋል።

ቡድኑ በሻዕቢያ ተቀጥሮ ኢትዮጵያን የባህር በር ያሳጣ ከሀዲ ነው በማለት ገልጸው፤ ኑ እንታረቅ ብሎ ፖለቲካ ድርጅትን በእርቅ መድረክ ያረደና ሰሜን ዕዝ ላይም ይህንን የደገመ ከሃዲ ቡድን ነው ሲሉ አብራርተዋል።

አሁንም በየቀኑ እየካደ ያለና በኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠረ የክህደት ኃይል እንደሆነም ጠቅሰዋል።

ይህ ኃይል እስካልተነቀለ ድረስ ኢትዮጵያ ሰላም አታገኝም ሲሉም አመልክተዋል።

 

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.