Fana: At a Speed of Life!

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ቀብር ሥነ ሥርዓት ነገ ይፈጸማል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 1 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ቀብር ሥነ ሥርዓት በነገው ዕለት ይፈጸማል፡፡

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) አስከሬን ሽኝት መርሐ ግብር ነገ 5 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ እንደሚካሄድ ተመላክቷል፡፡

ሥርዓተ ቀብራቸውም ነገ 7 ሰዓት ላይ በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር እንደሚፈጸም አስተባባሪ ኮሚቴው ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ባደረባቸው ሕመም ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በትናንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወቃል፡፡

ላጲሶ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ የታሪክ ጥናትና ምርምር በማካሄድ የተለያዩ የታሪክ መጽሐፍትን ለአንባቢያን አበርክተዋል፡፡

የኢትዮጵያውያንን የጋራ እሴት፣ ባሕልና ቋንቋ በማውሳት የሕዝቦች ታሪክ ጎልቶ እንዲታወቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውም ተጠቁሟል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.