በመዲናዋ ሕገ ወጥ የእንስሳት እርድን ለመከላከል በቅንጅት እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ የሚስተዋለውን ሕገ ወጥ የእንስሳት እርድ ለመከላከል እየተሰራ ነው አለ የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን።
በከተማዋ እየተባባሰ በመጣው ሕገ ወጥ እርድ፣ የስጋና የእንስሳት ዝውውር ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ አዲስ አበባን ምቹና ለኑሮ ተስማሚ እንድትሆን የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።
የመዲናዋን ልማትና ውበት ለማጠናከርም በተለያዩ ዘርፎች የሚስተዋሉ ሕገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በሕገ ወጥ እርድ፣ መሬት ወረራ፣ ሕገ ወጥ ንግድ፣ አዋኪ ተግባራት፣ ሕገ ወጥ ማስታወቂያና በሌሎች የደንብ ጥሰቶች ላይ አስፈላጊው ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ የኮንፈረንስና የቱሪስት ማዕከል ከመሆኗ ጋር ተያይዞ ለእንግዶች ደረጃውን የጠበቀ እርድ ማከናወን እንደሚገባም አመልክተዋል።
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ በበኩላቸው÷ ጤንነቱ የተጠበቀ አስተማማኝ የእርድ አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው ብለዋል።
ይሁን እንጂ በከተማ አስተዳዳሩ በየመንደሩ የሚደረግ ሕገ ወጥ የእንስሳት እርድ ሒደት እየተስፋፋ መሆኑን ገልጸዋል።
የእንስሳት እርድ በሕክምና ባለሙያዎች ተመርምሮ ጤንነቱ ከተረገጋጠ በኋላ ሕጋዊ እርድ በሚከናወንባቸው ቦታዎች ላይ መፈጸም አለበት ነው ያሉት።
ሕገ ወጥ እርድን ለመከላከልም የሚመለከታቸው አካላት በትኩረትና በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን፣ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት፣ የከተማ ግብርና ኮሚሽን፣ የሆቴል ባለቤቶች እንዲሁም የልኳንዳ ነጋዴዎች ማህበር ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በመላኩ ገድፍ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!