Fana: At a Speed of Life!

የባቡር ትራንስፖርት ለቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባቡር ትራንስፖርት እንቅስቃሴ ለቱሪዝም ዘርፉ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል አሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)።

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አ.ማ ጋር በመተባበር ከሚዲያ ተቋማት ባለሙያዎችና ከማሕበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጋር በቤኑና መንደር ጉብኝት እያካሄደ ሲሆን÷ የባቡር ትራንስፖርትን ለቱሪዝም ያለው ሚና በሚል ሐሳብ የባቡር ቱሪዝም ስራ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።

ሚኒስትር ዴዔታው ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ ከኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር አ.ማ ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ያላትን የቱሪዝም ጸጋዎች የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ ነው፡፡

የባቡር ትራንስፖርት ለቱሪዝም ዘርፍ ያለው አበርክቶ ተቋማዊ እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው÷ ቱሪዝምን ያለትራንስፖርት ማሰብ አይቻልም ብለዋል።

ከዚህ ቀደም የባቡር ትራንስፖርትን በአግባቡ እየተጠቀምን አልነበረም ያሉት ሚኒስትር ዴዔታው÷ ባቡርን ከቱሪዝም ጋር በማቀናጀት አማራጭ፣ ፈጣን እና ምቹ በሆነ መንገድ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡

የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር የተለያዩ ክልሎችና የቱሪስት መዳረሻዎችን እንደሚያካልል ጠቅሰው÷ ይህም ለቱሪዝም ከፍተኛ አቅም እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በቀጣይ የባቡር ቱሪዝምን ከማስተዋወቅ በተጨማሪ የቱሪዝም መሰረተ ልማቶችን የማልማት ስራዎች ይከናወናሉም ነው ያሉት፡፡

የዛሬው ጉዞ በአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑን አንስተው÷ ባቡር በራሱ የቱሪዝም ስበት ማዕከል እንደሆነ እና የቱሪዝም መዳረሻዎችን ከባቡር መስመር ጋር ለማገናኘት እቅድ መያዙን ጠቁመዋል።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.