Fana: At a Speed of Life!

አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር ዛሬ ምሽት ከብሬንትፎርድ ጋር ይጫወታል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል የሊጉን መሪነት ለማጠናከር ዛሬ ምሽት ብሬንትፎርድን በሜዳው ያስተናግዳል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ትናንት ምሽት ፉልሃምን 5 ለ 4 ማሸነፉን ተከትሎ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ማጥበብ ችሏል፡፡

መድፈኞቹ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ ለማድረግ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ከ30 በሚደረገው ጨዋታ ብሬንትፎርድን ማሸነፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ሁለቱ ክለቦች በፕሪሚየር ሊጉ እርስ በርስ ባደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል ሦስቱን ሲያሸንፍ፥ በሁለቱ አቻ ተለያይተዋል፡፡

በሌሎች የዛሬ ምሽት ጨዋታዎች በፕሪሚየር ሊጉ ከሁለት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰው ሊቨርፑል ምሽት 5 ሰዓት ከ15 ሰንደርላንድን የሚገጥምበት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በተመሳሳይ 5 ሰዓት ከ15 በሊጉ ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ቼልሲ ከሜዳው ውጭ ሊድስ ዩናይትድን የሚገጥም ሲሆን፥ ብራይተን ከአስቶን ቪላ፣ በርንሌይ ከክሪስታል ፓላስ እንዲሁም ወልቭስ ከኖቲንግሃም ፎረስት ምሽት 4 ሰዓት ከ30 ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

በአቤል ነዋይ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.